| ← Nehemiah (7/13) → | 
| 1. | እንዲህም ሆነ፤ ቅጥሩ ከተሠራ በኋላ፥ ሳንቃዎቹንም ካቆምሁ በኋላ፥ በረኞቹና መዘምራኑ ሌዋውያኑም ከተሾሙ በኋላ፥ | 
| 2. | ወንድሜን አናኒንና የግንቡን አለቃ ሐናንያን በኢየሩሳሌም ላይ ሾምኋቸው፤ እርሱም እውነተኛ ከሌሎቹም ይልቅ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ነበረ። | 
| 3. | እኔም። ፀሐይ እስኪሞቅ ድረስ የኢየሩሳሌም በሮች አይከፈቱ፤ እነርሱም ቆመው ሳሉ ደጆቹን ይዝጉ፥ ይቈልፉም፤ ከኢየሩሳሌምም ሰዎች አንዳንዱን በየተራው አንዳንዱንም በየቤቱ አንጻር ጠባቆችን አስቀምጡ አልኋቸው። | 
| 4. | ከተማይቱም ሰፊና ታላቅ ነበረች፤ በውስጥዋ የነበሩ ሕዝብ ግን ጥቂቶች ነበሩ፥ ቤቶቹም አልተሠሩም ነበር። | 
| 5. | አምላኬም ታላቆቹንና ሹማምቱን ሕዝቡንም ሰብስቤ እቈጥራቸው ዘንድ በልቤ አደረገ፤ አስቀድመው የመጡትን ሰዎች የትውልድ መጽሐፋቸውን አገኘሁ፥ በእርሱም እንደዚህ ተጽፎ አገኘሁ። | 
| 6. | የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ከማረካቸው ምርኮኞች ወደ ኢየሩሳሌምና ወደ ይሁዳ ወደ እየከተማቸው የተመለሱት የአገር ልጆች እነዚህ ናቸው። | 
| 7. | ከዘሩባቤል፥ ከኢያሱ፥ ከነህምያ፥ ከአዛርያስ፥ ከረዓምያ፥ ከነሐማኒ፥ ከመርዶክዮስ፥ ከበላሳን፥ ከሚስጴሬት፥ ከበጉዋይ፥ ከነሑም፥ ከበዓና ጋር መጡ። | 
| 8. | የእስራኤልም ሕዝብ ሰዎች ቍጥር ይህ ነው፤ የፋሮስ ልጆች፥ ሁለት ሺህ መቶ ሰባ ሁለት። | 
| 9. | የሰፋጥያስ ልጆች ሦስት መቶ ሰባ ሁለት። | 
| 10. | የኤራ ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ ሁለት። | 
| 11. | ከኢያሱና ከኢዮአብ ልጆች የሆኑ የፈሐት ሞዓብ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስምንት መቶ አሥራ ስምንት። | 
| 12. | የኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። | 
| 13. | የዛቱዕ ልጆች፥ ስምንት መቶ አርባ አምስት። | 
| 14. | የዘካይ ልጆች፥ ሰባት መቶ ስድሳ። | 
| 15. | የቢንዊ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ስምንት። | 
| 16. | የቤባይ ልጆች፥ ስድስት መቶ ሀያ ስምንት። | 
| 17. | የዓዝጋድ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ሀያ ሁለት። | 
| 18. | የአዶኒቃም ልጆች፥ ስድስት መቶ ስድሳ ሰባት። | 
| 19. | የበጉዋይ ልጆች፥ ሁለት ሺህ ስድሳ ሰባት። | 
| 20. | የዓዲን ልጆች፥ ስድስት መቶ አምሳ አምስት። | 
| 21. | የሕዝቅያስ ወገን የአጤር ልጆች፥ ዘጠና ስምንት። | 
| 22. | የሐሱም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ ስምንት። | 
| 23. | የቤሳይ ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ አራት። | 
| 24. | የሐሪፍ ልጆች፥ መቶ አሥራ ሁለት። | 
| 25. | የገባዖን ልጆች፥ ዘጠና አምስት። | 
| 26. | የቤተ ልሔምና የነጦፋ ሰዎች፥ መቶ ሰማንያ ስምንት። | 
| 27. | የዓናቶች ሰዎች፥ መቶ ሀያ ስምንት። | 
| 28. | የቤትዓዝሞት ሰዎች፥ አርባ ሁለት። | 
| 29. | የቂርያትይዓሪምና የከፊራ የብኤሮትም ሰዎች፥ ሰባት መቶ አርባ ሦስት። | 
| 30. | የራማና የጌባ ሰዎች፥ ስድስት መቶ ሀያ አንድ። | 
| 31. | የማክማስ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሁለት። | 
| 32. | የቤቴልና የጋይ ሰዎች፥ መቶ ሀያ ሦስት። | 
| 33. | የሁለተኛው ናባው ሰዎች፥ አምሳ ሁለት። | 
| 34. | የሁለተኛው ኤላም ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አምሳ አራት። | 
| 35. | የካሪም ልጆች፥ ሦስት መቶ ሀያ። | 
| 36. | የኢያሪኮ ልጆች፥ ሦስት መቶ አርባ አምስት | 
| 37. | የሎድና የሐዲድ የኦኖም ልጆች፥ ሰባት መቶ ሀያ አንድ። | 
| 38. | የሴናዓ ልጆች፥ ሦስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሠላሳ። | 
| 39. | ካህናቱ፤ ከኢያሱ ወገን የዮዳኤ ልጆች፥ ዘጠኝ መቶ ሰባ ሦስት። | 
| 40. | የኢሜር ልጆች፥ ሺህ አምሳ ሁለት። | 
| 41. | የፋስኮር ልጆች፥ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት። | 
| 42. | የካሪም ልጆች፥ ሺህ አሥራ ሰባት። | 
| 43. | ሌዋውያኑ፤ ከሆዳይዋ ወገን የኢያሱና የቀድምኤል ልጆች፥ ሰባ አራት። | 
| 44. | መዘምራኑ፤ የአሳፍ ልጆች፥ መቶ አርባ ስምንት። | 
| 45. | በረኞቹ፤ የሰሎም ልጆች፥ የአጤር ልጆች፥ የጤልሞን ልጆች፥ የዓቁብ ልጆች፥ የሐጢጣ ልጆች፥ የሶባይ ልጆች፥ መቶ ሠላሳ ስምንት። | 
| 46. | ናታኒም፥ የሲሐ ልጆች፥ የሐሡፋ ልጆች፥ | 
| 47. | የጠብዖት ልጆች፥ የኬራስ ልጆች፥ የሲዓ ልጆች፥ | 
| 48. | የፋዶን ልጆች፥ የልባና ልጆች፥ | 
| 49. | የአጋባ ልጆች፥ የሰምላይ ልጆች፥ የሐናን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥ የጋሐር ልጆች፥ | 
| 50. | የራያ ልጆች፥ የረአሶን ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ | 
| 51. | የጋሴም ልጆች፥ የዖዛ ልጆች፥ የፋሴሐ ልጆች፥ | 
| 52. | የቤሳይ ልጆች፥ የምዑናውያን ልጆች፥ | 
| 53. | የንፉሰሲም ልጆች፥ የበቅቡቅ ልጆች፥ የሐቀፋ ልጆች፥ የሐርሑር ልጆች፥ | 
| 54. | የበስሎት ልጆች፥ የምሒዳ ልጆች፥ የሐርሻ ልጆች፥ | 
| 55. | የበርቆስ ልጆች፥ የሲሣራ ልጆች፥ | 
| 56. | የቴማ ልጆች፥ የንስያ ልጆች፥ የሐጢፋ ልጆች። | 
| 57. | የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች፤ የሶጣይ ልጆች፥ የሶፌሬት ልጆች፥ የፍሩዳ ልጆች፥ | 
| 58. | የየዕላ ልጆች፥ የደርቆን ልጆች፥ የጌዴል ልጆች፥ | 
| 59. | የሰፋጥያስ ልጆች፥ የሐጢል ልጆች፥ የፈከራት ልጆች፥ የሐፂቦይም ልጆች፥ የአሞን ልጆች። | 
| 60. | ናታኒም ሁሉና የሰሎሞን ባሪያዎች ልጆች ሦስት መቶ ዘጠና ሁለት ነበሩ። | 
| 61. | ከቴልሜላ፥ ከቴላሬሳ፥ ከክሩብ፥ ከአዳን፥ ከኢሜር የወጡ እነዚህ ናቸው፤ ነገር ግን የአባቶቻቸውን ቤቶችና ዘራቸውን ወይም ከእስራኤል ወገን መሆናቸውን ያስታውቁ ዘንድ አልቻሉም፤ | 
| 62. | የዳላያ ልጆች፥ የጦብያ ልጆች፥ የኔቆዳ ልጆች፥ ስድስት መቶ አርባ ሁለት። | 
| 63. | ከካህናቱም የኤብያ ልጆች፥ የአቆስ ልጆች፥ ከገለዓዳዊው ከቤርዜሊ ልጆች ሚስት ያገባ በስሙም የተጠራ የቤርዜሊ ልጆች። | 
| 64. | እነዚህ በትውልድ መጽሐፍ ትውልዳቸውን ፈለጉ፥ ነገር ግን አልተገኘም፤ ከክህነትም ተከለከሉ። | 
| 65. | ሐቴርሰታም። በኡሪምና በቱሚም የሚፈርድ ካህን እስኪነሣ ደረስ ከተቀደሰው ነገር አትበሉም አላቸው። | 
| 67. | ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ሠላሳ ሰባት ከነበሩ ከሎሌዎቻቸውና ከገረዶቻቸው ሌላ ጉባኤው ሁሉ አርባ ሁለት ሺህ ሦስት መቶ ስድሳ ነበሩ፤ ሁለቱ መቶም አርባ አምስት ወንዶችና ሴቶች መዘምራን ነበሩአቸው። | 
| 68. | ፈረሶቻቸውም ሰባት መቶ ሠላሳ ስድስት፥ በቅሎቻቸውም ሁለት መቶ አርባ አምስት፥ | 
| 69. | ግመሎቻቸውም አራት መቶ ሠላሳ አምስት፥ አህዮቻቸውም ስድስት ሺህ ሰባት መቶ ሀያ ነበሩ። | 
| 70. | ከአባቶች ቤቶች አለቆችም አያሌዎቹ ሰዎች ስለ ሥራው ስጦታ ሰጡ። ሐቴርሰታም አንድ ሺህ የወርቅ ዳሪክ፥ አምሳም ድስቶች፥ አምስት መቶ ሠላሳም የካህናት ልብስ በቤተ መዛግብት ውስጥ ሰጠ። | 
| 71. | ከአባቶች ቤቶች አለቆችም አያሌዎቹ በሥራው ቤተ መዛግብት ውስጥ ሀያ ሺህ የወርቅ ዳሪክ፥ ሁለት ሺህ ሁለት መቶም ምናን ብር ሰጡ። | 
| 72. | የቀሩትም ሕዝብ የሰጡት ሀያ ሺህ የወርቅ ዳሪክና ሁለት ሺህ ምናን ብር፥ ስድሳ ሰባትም የካህናት ልብስ ነበረ። | 
| 73. | ካህናቱና ሌዋውያኑም፥ በረኞቹና መዘምራኑም ከሕዝቡም አያሌዎቹ፥ ናታኒምም፥ እስራኤልም ሁሉ በከተሞቻቸው ተቀመጡ። | 
| ← Nehemiah (7/13) → |